ማበልጸጊያዎች ስራ መጀመር እንደትችሉ ሊረዷችሁ የሚችሉ አቃፊ ተቋሞች አዲስ አበባ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ለበለጠ መረጃ ድረ-ገጾቻቸውን ጎብኙ፡፡ አይ.ሲ.ቲ.ፓርክ200 ሄክታር ላይ ያረፈዉ አይ.ሲ.ቲ. ፓርክ አዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ከቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀርባ ይገኛል፡፡ የመሥሪያ ቦታን ጨምሮ ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት፣ በቂ የኤሌክትሪከ ኃይል አቅርቦት፣ አስተማማኝ የዳታ ደህንነት፣ መሬት በተመጣጣኝ ዋጋ እና ተያያዥ አገልግሎቶችን በተጨማሪም የተለያዩ ማበረታቻዎችን ያቀርባል፡፡ የገንዘብና የፋይናንስ አገልግሎቶችን ጨምሮ የአንድ መስኮት የመንግስት አገልግሎቶች የሚሠጡ ተቋማት ይገኛሉ፡፡ እስከአሁን ከ70 በላይ የኢ.ኮ.ቴ ኩባንያዎች ወደ ፓርኩ ገብተዋል፡፡አይስ አዲስበ2011 የተቋቋመው አይስ አዲስ ለጀማሪ የኢ.ኮ.ቴ ድርጅቶች ስልጠና እና የጋራ መስሪያ ቦታ ያማቻቻል፡፡ ድረ-ገፅ ብሉ ሙንብሉ ሙን በ2017 የተመሠረተ አቃፊ ሲሆን በዓመት ሁለት ጊዜ በሚያደርገው አገር ዓቀፍ ውድድር የሚደግፋቸውን ጀማሪ ድርጅቶችን ይመርጣል፡፡ የተመረጡ ጀማሪዎች ስልጠና፣ የቢዝነስ ማበልጸፀጊያ ድጋፍ፣ የመሥሪያ ቦታ፣ እና የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበት ሁኔታ ይመቻችላቸዋል፡፡ ድረ-ገፅ ዘ ኤስክ ሀብበአፍሪካ የአመራር ጥናት ማዕከል በ2014 የተጀመረው ይህ አቃፊ ድርጅት ጀማሪ ድርጅቶች ኃሳባቸውን ወደ ተጨባጭ ቢዝነሶችና አገልግሎቶች እንዲያሸጋግሩ ያማክራል፣ ይድግፋል ፡፡ ይኼንንም ለማሳካት የሥልጠና እና የጋራ መስሪያ ቦታ ያቀርባል፡፡ ድረ-ገፅ ኮሚሽኑ ስለ እኛ የትኩረት መስኮች ተባባሪዎች የቅንጅት መድረክ ለሥራ ፈላጊዎች ለሥራ አመልክቱ ጥቆማዎች የቅጥር አገልግሎቶች የኢንዱስትሪ ፓርኮች ሥራ ፈጠሪዎች ሥራ ለሰሪው ማበልጸጊያዎች የገንዘብ ድጋፍ ሰጪዎች ድርጅቶችን ማጎልበት ትሥሥር ለመፍጠር ውድድሮች ድጋፍ ቁልፍ ስታቲስቲክስ የቅጥር ሁኔታ አመላካች ቁልፍ ስታቲስቲክስ እኛን ለማግኘት ይፃፉልን አድራሻችን የባለቤትነት መብት © 2021 የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ኢትዮጵያ ፥ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።